የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ ጋዜጠኞች ማህበር (EJPWD) ከCARD ባገኘው የገነዘብ ድጋፍ “አካታች ሚዲያ እና የሰብአዊ መብት ግንዛቤ ማሳደግ ፕሮጀክት” መጀመሩን በደስታ እናጋራለን።
ፕሮጀክቱ ለ3 ተከታታይ ወራት ማለትም
ይህ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ ውስጥ አካታች የሚዲያ ስራን ለማጠናከር በማሰብ የተዘጋጀ ሲሆን ጋዜጠኞችን በሰብአዊ መብት መሰረት ያለ እና አካል ጉዳትን አካታች የሆነ ሪፖርቲንግ ላይ ማጠናከር፣ የህዝብ ግንዛቤን ማሳደግ እና የማህበረሰብ ውይይቶችን ማበረታታት ይዘው ይመጣል።
በፕሮጀክቱ ውስጥ የሚካተቱ ዋና እንቅስቃሴዎች፦
- 20 ጋዜጠኞችን በአካል ጉዳት አካታች እና በሰብአዊ መብት ሪፖርቲንግ ላይ ማሰልጠን
- በአማርኛ 2 የሬዲዮ የግንዛቤ መልዕክቶችን ማምረት እና ማሰራጨት
- 3 ዲጂታል የሚዲያ ይዘቶችን ማምረት
- አካል ጉዳተኞች፣ ጋዜጠኞች እና የማህበረሰብ ተወካዮች የሚሳተፉበት የህዝብ ውይይት ማካሄድ
ይህ ፕሮጀክት የአካል ጉዳት መብቶች ላይ ያለውን የህዝብ ግንዛቤ ለማሳደግ፣ የመረጃ ተደራሽነትን ለማሻሻል እና በማህበራዊ እና ዲሞክራሲያዊ ሂደቶች ውስጥ አካታች ተሳትፎን ለማበረታታት ያግዛል።
አካታች ሚዲያ ያለው ማህበረሰብ አካታች ይሆናል።